ጀርመን የሊግ የእግር ኳስ ውድድሮችን መልሶ በማስጀመር የመጀመሪያዋ ሆነች
መጋቢት 02/2012 ዓ.ም፡ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሁሉም ጨዋታዎች እንዳይካሄዱ ከመደረጉ በፊት የቡንደስ ሊጋው የመጨረሻ ጨዋታ በቦሪሲያ ሞንቼግላድባህ እና በኮለን መካከል በዝግ ስታዲየም ነበር የተደረገው።
ግንቦት 08/2012 ዓ.ም፡ የቡንደስ ሊጋ ውድድር ተጀምሯል። በወረርሽኙ ምክንያት የእግር ኳስ ውድድሮች በመላው ዓለም እንዲቋረጡ ከተደረጉ በኋላ፤ ጀርመን የሊግ ጨዋታዎችን መልሳ በመጀመር በአውሮፓ የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች። ቦሩሲያ ዶርትመንድ ከሻልከ የሚያደርጉት የደርቢ ጨዋታ የውድድሩን መጀመር ያበስራል ተብሏል።