ፕሪምየር ሊጉ በልምምድ ወቅት ‘ታክል’ መውረድ ሊከለከል ነው
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግን ለማስጀመር በርካታ ቅድመ ሁኔታዎች ቀርበዋል። ከእነዚህም መካከል በልምምድ ወቅት ታክል መውረድ መከልከሉና ሜዳዎቹ በጸረ ቫይረስ መድኃኒቶች እንዲረሸጩ ግዴታ መሆኑ ይገኙበታል። በተጨማሪም የእግር ኳስ ተጫዋቾች ልምምድ ሲያደርጉየ ከአምስት በላይ መሆን አይችሉም ተብሏል። የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የሚጀመር ከሆነ ተጫዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ የሚደረግላቸው ሲሆን ከስልጠና በፊት ቃለመጠይቅና የሙቀት ልኬትም ግዴታዎች ናቸው።