አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ዛሬ በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር በርቀቱ በመጀመሪያ ተሳትፎዋ በአሸናፊነት አጠናቀለች።
አትሌቷ ግማሽ ማራቶኑን ለማጠናቀቅ የገባችበት 1፡05፡18 ሰአት የውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
ሌለኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ ርቀቱን 1፡05፡51 ሰአት በማጠናቀቅ 3ኛ ሆና ገብታለች።
ኬንያዊቷ ሼይላ ቼፕኩሪ ውድድሩን 2ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።
ዛሬ በቫሌንሺያ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በወንዶች ኢትዮጵያዊው አትሌት ብርሃኑ ለገሰ 3ኛ ደረጃ መያዝ አጠናቋል።
ኬኒያዊያዊያኑ ቼቤት እና ቼርኖኖ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል።