• ሼፍልድ ዩናይትድ ያልተጠበቀ ሶስት ነጠብ ከ ኦልድ ትራፎርድ ይዘው ሲመለሱ አሸናፊ የሆኑበትን ግብ በ ኪን ብራየን እና ኦሊቨር ቡርክ አማካኝነት አግኝተዋል ።
• የ ዩናይትድን ብቸኛ ግብ ሀሪ ማጓየር ከመረብ ማሳረፍ ቢችልም ከሽንፈት ሊታደጋቸው አልቻለም ።
• ቶማስ ቱሄል እና ቼልሲ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ከ ዎልቭስ ጋር ሲያደርጉ በአቻ ውጤት ጀምረዋል ።
• ሼፍልድ ዩናይትድ በሊጉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦልድ ትራ ፎርድ ድል ማድረግ ችለዋል ።
• የምሽቱን ድል ተከትሎ ሼፍልድ የ ዩናይትድ የ አስራ ሶስት ጨዋታ ያለመሸነፍ ጉዞ ረተዋል ።
• ጁቬንቱስ በ ፍራቦታ ፣ ኬዛ ፣ ሞራታ እና ኩሉሴቪስኪ ጎሎች ስፓልን በማሸነፍ በኮፓ ኢታሊያ ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል ።
• ጁቬንቱስ በቀጣይ ዙር ከ ኢንተር ሚላን ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ።
• የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በ ሜሲ እና ዲዮንግ ግቦች ራዮ ቫይካኖን 2 ለ 1 በማሸነፍ በ ኮፓ ዴ ላሬ ቀጣዩን ዙር መቀላለቀላቸውን አረጋግጠዋል ።
• ሊዮኔል ሜሲ በ ኮፓ ዴ ላሬ ያስቆጠራቸውን የግብ መጠን ወደ 54 ከፍ ማድረግ ችሏል ።