የለንደኑ ክለብ ቼልሲ ኒውካስትልን በ ቲሞ ቨርነር እና ጅሩድ ጎሎች በማሸነፍ በድል ጉዟቸው በመቀጠል ደረጃቸውን ከፍ ማድረግ ችለዋል ።
• ቼልሲ በቶማስ ቱሄል ስር ከስድስት ጨዋታዎች በአምስቱ መረባቸውን አላስደፈሩም ።
• ቼልሲዎች ባለፉት ሀያ ቀናት ከነበሩበት አስረኛ ደረጃ ወደ አራተኛ ከፍ ማለት ችለዋል ።
• ከግብ ጋር ተራርቆ የቀፐየው ቲሞ ቨርነር ከ 100 ቀናት በኋላ ወደ ግብ አግቢነቱ መመለስ ችሏል ።
• ቲሞ ቨርነር በዘንድሮው የውድድር ዓመት በአስር ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎን ማድረግ ችሏል ።
• ሌላኛውን ግብ ያስቆጠረው ኦሊቪዬ ጅሩ በሊጉ ተቀይሮ በመግባት 100ኛ ጨዋታውን ማካሄድ ችሏል ።
• ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ ወደ አራተኛ ደረጃ ከፍ ብለዋል ።