በፈረንሳይ ቫል ዴ ሪዩል በተካሄደው የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ጉዳግፍ በዚያው በፈረንሳይ ክብረ ወሰን ከሰበረች በሳምንት ውስጥ ሁለተኛ ድሏን 800 ሜትር አሸንፋለች።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እ.አ.አ ከ2006 ወዲህ ርቀቱን 1:57.52 በሆነ ጊዜ የአለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ነው ለማሸነፍ የቻለችው።
አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ በ1500 ሜትር የመሰናክል ሩጫ ለሜቻ ግርማን አስከትሎ በመግባት ሌላ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል።
አትሌት ጌትነት ዋለ 1500 ሜትሩን በ3:35.54 ጊዜ ሲጨርስ ፣ አትሌት ለሜቻ ግርማ ደግሞ 3:35.60 በሆነ ጊዜ ሁለተኛ ሆኖ በማጠናቀቅ የሳምንቱን ድል ለኢትዮጵያ ያማረ እንዲሆን አድርጎታል።