ቀያይ ሴጣኖቹ በ ኦልድ ትራ ፎርድ ባደረጉት ጨዋታ ክሬግ ዳውሰን በራሱ ላይ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ዌስትሀምን ማሸነፍ ችለዋል ።
• ማክቶሚናይ በዘንድሮው የውድድር ዓመት የመጀመሪያ የቢጫ ካርዱን በዛሬው ጨዋታ ተመልክቷል ።
• ማክቶሚናይ ሰላሳ ሶስት ጥፋቶችን እስከ አሁን ሲሰራ አንድም የማስጠንቀቂያ ካርድ አልተመለከተም ነበር ።
• ዌስትሀሞች ቀድመው በተመሩባቸው ያለፉት አስራ ሰባት ጨዋታዎች ቀያይ ሴጣኖቹን ማሸነፍ አልቻሉም ።
• ለቀያይ ሴጣኖቹ ኤቨርተን ፣ ቼልሲ እና ቶተንኋሀም በሳምንቱ ነጥብ መጣላቸው ጥሩ አጋጣሚ ሆኖ አልፎላቸዋል ።
• ማንችስተር ዩናይትድ ከዛሬ ተጋጣሚያቸው ዌስትሀም በዘጠኝ ነጥቦች እንዲሁም ከ ቶተንሀም በ አስራ ሁለት ነጥቦች ርቀዋል ።
• ማንችስተር ዩናይትዶች ድሉን ተከትሎ በደረጃ ሰንጠረዡ ሁለተኛ ደረጃን ከ ሌስተር ሲቲ ተረክበዋል ።