• የለንደኑ ክለብ ቼልሲ በአስደናቂ ብቃታቸው ሲቀጥሉ የላሊጋውን መሪ አትሌቲኮ ማድሪድ በኤመርሰን እና ዚያች ጎል አሸንፈዋል ።
• ሙኒክ በተመሳሳይ ሁኔታ ላዚዮን በ ሊዋንዶውስኪ እና ሞቲንግ ጎሎች በማሸነፍ በቀላሉ ቀጣዩን ዙር ተቀላቅለዋል ።
• አትሌቲኮ ማድሪድ ባለፉት አስር ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት በሶስቱ ብቻ ነው ።
• ንጎሎ ካንቴ እና ጆሽዋ ኪሚክ የምሽቱ ጨዋታ ኮከብ በመባል ተመርጠዋል ።
• የቼልሲው ግብ ጠባቂ ሜንዲ በሻምፒየንስ ሊጉ ከተሞከሩበት ሀያ ሙከራዎች አስራ ዘጠኙን ማዳን ችሏል ።
• ሜንዲ ከዚህ በተጨማሪም በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ካደረጋቸው ሰባት ጨዋታዎች በስድስቱ መረቡን አላስደፈረም ።
• ባየር ሙኒክ ወደ ሩብ ፍፃሜው ለአስራ ዘጠነኛ ጊዜ ማለፋቸውን ተከትሎ በውድድሩ ታሪክ የመጀመሪያው ቀዳሚ ክለብ ሆነዋል ።
• ቼልሲዎች ቶማስ ቱሄል ቡድኑን ከተረከቡ በኋላ ባደረጓቸው አስራ ሶስት ጨዋታዎች ባለ መሸነፍ ቀጥለዋል ።
• ሪያል ማድሪድ ብቸኛው የላሊጋው ተወካይ በመሆን በሩብ ፍፃሜው የሚሳተፍ ይሆናል ።
• የቼልሲው ኤመርሰን ያስቆጠራት ግብ በሻምፒየንስ ሊጉ ታሪክ የተቆጠረችው 9,000ኛ ጎል ሆናለች ።