የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በኦሊምፒክ እና በሌሎች ውድድር መድረኮች ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ላደረገችው ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ሀገር አቀፍ የክብር የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶላታል።
350 ግራም የሚመዝነውን የወርቅ ኒሻን ሽልማቱን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አበርክተውላታል።
ከኒሻኑ በተጨማሪም 2021 ሞዴል የሆነች ሌክሰስ ቪ8 መኪና በአገር አቀፍ ደረጃ ተበርክቶላታል።
ለደራርቱ ቱሉ አገር አቀፍ የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም ተካሂዷል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከክብር ሽልማቱ እና ከመኪናው በተጨማሪ የተለያዩ ሽልማቶችም ተበርክተውላታል።