ከሳምንታት በፊት ከሜዳቸው ውጪ በዩሮፓ ሊጉ ግራናዳን ያሸነፉት ቀያይ ሴጣኖቹ ” ባልተገባ ፀባይ ” ምክንያት የገንዘብ ቅጣት እንደተላለፈባቸው ተሰምቷል ።
ዩናይትድ በዩሮፓ ሊጉ ግራናዳን ባሸነፉበት ጨዋታ አምስት የቢጫ ካርድ ማየታቸውን ተከትሎ የ 7,000 ፓውንድ ቅጣት እንደተጣለባቸው ታውቋል ።
በመረጃው እንደተገለፀው ዩናይትዶች የገንዘቡ ቅጣቱን በመጪው ዘጠና ቀናት መክፈል እንደሚኖርባቸው ተዘግቧል ።