ማንችስተር ሲቲ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2020/21 የውድድር ዓመት ሻምፒዮን መሆናቸውን አረጋገጡ።
ሲቲዎች ሻምፒዮን መሆናቸውን ያረጋገጡት ማንችስር ዩናይትድ በሜዳው በሌስተር ሲቲ 2 ለ 1 መሸነፉን ተከትሎ ነው።
ሊጉ ሊጠናቀቅ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ የቀሩት ሲሆን የደረጃ ሰንጠረዡን በሚመራው ማንችስተር ሲቲ እና ሁለተኛ ሆኖ በሚከተውለው ማንችስተር ዩናይትድ መካከል የ10 ነጥብ ልዩነት አለ።
ማንችስተር ዩናይትድ በቀሪ ጨዋታዎች ሲቲ ላይ እንደማይደርስ በመረጋገጡ ነው ሲቲዎች ሻምፒዮን መሆናቸውን ያረጋገጡት።