• ፈረንሳይ በአንቱዋን ግሪዝማን ድንቅ ግብ እና ኦሊቭዬ ጅሩ ሁለት ግቦች ቡልጋርያን አሸንፈዋል ።
• ከስድስት ዓመታት በኋላ ለ ፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ የቀረበለት ካሪም ቤንዜማ ተጎድቶ ከሜዳ ወጥቷል ።
• አርጀንቲና በ ሮሜሮ እና ፓሬዳስ ጎሎች በ ጊዜ መምራት ቢጀምሩም የኋላ ኋላ በተቆጠሩባቸው ጎሎች ሁለት አቻ ወጥተዋል ።
• አርጀንቲና በቀጣይ ሰኞ በ ኮፓ አሜሪካ የመክፈቻ ጨዋታ ቺሊን የምትገጥም ይሆናል ።
• ብራዚል በ ኮከቧ ኔይማር የአራተኛ ደቂቃ ግብ እና የ ሉካስ ፓኩዌታ ግብ ታግዘው ፓራጓይን 2 ለ 0 በማሸነፍ ስድስተኛ ተከታታይ ድላቸውን አስመዝግበዋል ።
• ብራዚል የደረጃ ሰንጠረዡን ከ ተከታያቸው አርጀንቲና በስድስት ነጥቦች ርቀው በአስራ ስምንት ነጥብ እየመሩ ይገኛሉ ።
*የግሪዝማን ጎል ከላይ ቢቪድዮው ተያይዟል ።