በጋሪዝ ቤል አምበልነት የሚመራው የዌልስ ብሄራዊ ቡድን የዘንድሮው የውድድር ዓመት የአውሮፓ ዋንጫ የመጀመሪያ ድላቸውን አስመዝግበዋል ።
• አሮን ራምሴ እና ሮበርትስ የ ዌልስን የማሸነፊያ ግብ በ ቱርክ ላይ ማሳረፍ ችለዋል ።
• ቱርክ ሁለተኛ የምድብ ሽንፈቷን ስታስተናግድ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ እድሏ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል ።
• ጋሪዝ ቤል በ ጨዋታው የ ዌልስን መሪነት ልታጠናክር የምትችል የፍፁም ቅጣት ምት በ ጨዋታው አምክኗል ።
• ዌልስ በቀጣይ የምድቡ የ መጨረሻ ጨዋታ ከ ጣልያን ጋር ወሳኝ መርሐ ግብራቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል ።