ኮከባቸውን ኬቨን ዴ ብሮይነ በሁለተኛው አጋማሽ ቀይረው ያስገቡት ቤልጅዬማዎች የጨዋታው ቀያሪ በመሆን ዴንማርክን ማሸነፍ ችለዋል ።
• ኬቨን ዴ ብሮይነ እና ቶርጋን ሀዛርድ የ ቤልጅዬምን የማሸነፊያ ጎሎች ማስቆጠር ችለዋል ።
• ዴ ብሮይነ በጨዋታው ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• የ ዴንማርክን ብቸኛ ግብ ያስቆጠረው የሱፍ ፖልሰን በዘንድሮው ውድድር ፈጣኑ ጎል ሆኖ ተመዝግቧል ።
• የሱፍ ፖልሰን ያስቆጠረው ግብ በአውሮፓ ዋንጫ ታሪክ ሶስተኛው ፈጣን ጎል ሆኖ ተመዝግቧል ።
• ቤልጅዬም በስድስት ነጥቦች ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል ።
• ጣልያን እና ቤልጅዬም ከወዲሁ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን ያረጋገጡ ብቸኞቹ ሀገራት ናቸው ።
• የመጨረሻው የምድብ ጨዋታ በጉጉት ሲጠበቅ ዴንማርክ ከ ሩሲያ እንዲሁም ፊንላንድ ከ ቤልጅዬም ጨዋታቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል ።