ወሳኝ ቁልፍ ተጫዋቿን ዶሚኒክ ስቦዝላይን በጉዳት ያጣችው ሀንጋሪ በደጋፊዎቿ ፊት ከ አለም ዋንጫ አሸናፊዋ ፈረንሳይ ጋር ነጥብ ተጋርታ መውጣት ችላለች ።
• ሀንጋሪን መሪ ያደረገች ግብ ያስቆጠረው አቲላ ፊዮላ ሁለተኛ ጎሉ ሆኖ ተመዝግቧል ።
• ከ 500 ደቂቃዎች በላይ ግብ ያላስተናገዱት ፈረንሳዮች በ ፊዮላ አማካኝነት ግብ ሊቆጠርባቸው ችሏል ።
• አንቱዋን ግሪዝማን በአውሮፓ ዋንጫው ሰባት ጎሎችን በማስቆጠር ከ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ሚሼል ፕላቲኒ በመቀጠል ሶስተኛው ከፍተኛ አግቢ ሆኗል ።
• ፖርቹጋል ከደቂቃዎች በኋላ ጀርመንን የምታሸንፍ ከሆነ በቀጥታ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን ታረጋግጣለች ።
• በቀጣይ የምድቡ ጨዋታዎች ፈረንሳይ ከ ፖርቹጋል እንዲሁም ሀንጋሪ ከ ጀርመን የሚጫወቱ ይሆናል ።