የ ኮፓ አሜሪካ የፍፃሜ ተፋላሚዎች ሲታወቅ ሌሊት በተደረገ መርሀ ግብር አርጀንቲና በመለያያ ምት ኮሎምቢያን በማሸነፍ ለፍፃሜ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል ።
• አርጀንቲና በፍፃሜው ከ አስተናጋጇ ሀገር ብራዚል ጋር በ ግዙፉ ማራካኛ ስታዲየም ቅዳሜ የሚጫወቱ ይሆናል ።
• ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ ለድሉ ቁልፍ ሚናን ሲጫወት ሶስት የመለያያ ምቶችን ማዳን ችሏል ።
• ሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና በ ኮፓ አሜሪካው ካስቆጠሩት አስራ አንድ ጎሎች መካከል በዘጠኙ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ አድርጓል ።