አስቀድመው በ ዳምስጋርድ ጎል መምራት የቻሉት ዴንማርኮች ሲሞን ካየር በራሱ ላይ እንዲሁም ኬን ባስቆጠረው ግብ ሽንፈት አስተናግደዋል ።
• ሀሪ ኬን በ ካስፐር ሽማይክል ላይ አስራ አምስተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል ።
• ሀሪ ኬን በ አውሮፓ ዋንጫው ያስቆጠራቸውን የ ግብ መጠን ወደ አራት ከፍ አድርጓል ።
• በአውሮፓ ዋንጫው በራስ ላይ የተቆጠሩ የግብ መጠን ወደ አስራ አንድ ከፍ ብለዋል ።
• እንግሊዝ በ ዘንድሮው የ አውሮፓ ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ግብ ተቆጥሮባቸዋል ።
• ጆርዳን ፒክፎርድ ከ 480 ደቂቃዎች በኋላ ግብ ሊቆጠርበት ችሏል ።
• እንግሊዝ በ አለም አቀፍ ውድድሮች ለ ፍፃሜ ስትደርስ ከ ሀምሳ አምስት ዓመታት በኋላ ነው ።
• እንግሊዝ በ ፍፃሜው በ ዌምብሌይ ስታዲየም የፊታችን እሁድ ምሽት ጨዋታቸውን ከ ጣልያን ጋር የሚያካሂዱ ይሆናል ።