Home Sport News ጣሊያን እንግሊዝን በማሸነፍ የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊ ሆነች

ጣሊያን እንግሊዝን በማሸነፍ የአውሮፓ ዋንጫ አሸናፊ ሆነች

by sam

ዛሬ ምሽት በተከናወነው የአውሮፓ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ጣሊያን እንግሊዝን በመለያ ምት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችላለች::

ለንደን በሚገኘው ግዙፉ የዌምብሌይ ስታዲየም በተደረገው የፍፃሜ  ጨዋታ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን በመለያ ምት ነው  3ለ2 ያሸነፈው::

የሁለቱ ቡድኖች መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ  አንድ  እኩል የተጠናቀቀ ሲሆን ለእንግሊዝ ሉክ ሾው እንዲሁም ለጣሊያን ሊዮናርዶ ቦኑቺ አስቆጥረዋል::

ሉክ ሾው ገና ጨዋታው እንደተጀመረ ሁለተኛው ደቂቃ ላይ ለእንግሊዝ  ያስቆጠራት ጎል በአውሮፖ ዋንጫ  ታሪክ ፈጣኗ ጎል በመባል ተመዝግባለች::

በውድድሩ ባሳየችው ድንቅ የጨዋታ አቀራረብ የዘንድሮውን ውድድር የማሸነፍ ቅድመ ግምት አግኝታ የነበረችው ጣሊያን የአውሮፓ ዋንጫን በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ ማሳካት ችላለች::

ጣሊያን በዚህ ውድድር ለመጀመሪያ  ጊዜ ዋንጫ ያሸነፈችው እአአ በ1968 ነበር::

በሜዳው የተጫወተው የእንግሊዝ ብሄራዊ  ቡድን  ለአውሮፓ ዋንጫ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያው ሲሆን    በ60ሺህ ደጋፊ ፊት  ተጫውቶ ዋንጫ  ማሸነፍ ሳይችል ቀርቷል::

እንግሊዝ እአአ 1966 ካሸነፈችው የአለም ዋንጫ ውጪ   ምንም ውድድር ላይ ሳይሳካላት 55 አመታት መቆጠራቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ::

የጣሊያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ የሆነው ጂያን ሉጂ ዶናሩማ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች  ሲሆን ክሪስቲያኖ ሮናልዶ እና የቼክ ሪፕብሊኩ  አጥቂ ፓትሪክ ሺክ  ደግሞ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ተጋርተዋል::

Leave a Comment

Related Posts

en_USEnglish