በ ቶኪዮ ኦሎምፒክ የ ወንዶች እግር ኳስ ጨዋታ ብራዚል ለ ተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን አረጋግጠዋል ።
120 ደቂቃዎች በፈጀው የ ፍፃሜ መርሐ ግብር ብራዚል በ ማቲየስ ኩና እና ማልኮም ግቦች ስፔንን 2 ለ 1 ማሸነፍ ችለዋል ።
የ ስፔንን ብቸኛ ግብ ኦይራዛባል ከመረብ ሲያሳርፍ የ ብር ሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን ችለዋል ።
በ ዳኒ አልቬስ አምበልነት የሚመራው የ ብራዚል የ ኦሎምፒክ ብሔራዊ ቡድን በ ሪዮ ኦሎምፒኩም የ ወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ እንደነበሩ ይታወሳል ።