ዛሬ በተካሄደው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ አርሰናልን 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡
ለማንችስተር ሲቲ ኤልካይ ጉንዶጋን በ7ኛው ደቂቃ፣ ፌራን ቶሬዝ በ12ኛው እና በ84ኛው ፣ ገብርኤል ጄሱስ በ43ኛው እና ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ በ53ኛው ደቂቃ ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡
በጨዋታው የአርሰናል የመሃል ሜዳ ተጫዋች ግራኒት ዣካ በሰራው ጥፋት በ35ኛው ደቂቃ ላይ ከሜዳ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል፡፡