ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለማንቼስተር ዩናይትድ ለመፈረም መስማማቱ ተሰማ፡፡
ፖርቹጋላዊው ተጫዋች ለማንቼስተር ሲቲ ይፈርማል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ቢሆንም ለማንቼስተር ዩናይትድ ለመፈረም ወስኗል።
ዩናይትድ ለ 36 አመቱ የአምስት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊ 12 ነጥብ 8 ሚሊየን ፓውንድ ለመክፈል ተስማምቷል፡፡
ሮናልዶ ከዚህ ቀደም በኦልድትራፎርድ ቆይታው በ292 ጨዋታዎች 118 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡