ደካማ የ ሴርያ ጅማሮን ያደረጉት ጁቬንቱሶች ሳምፕዶርያን 3 ለ 2 በ ማሸነፍ ደረጃቸውን ያሻሻሉበት ውጤት አስመዝግበዋል ።
• ፓውሎ ዲባላ ፣ ቦኑቺ እና ማኑኤል ሎካቴሊ የ ጁቬንቱስን የ ማሸነፊያ ጎሎች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው ።
• ማሲሚሊያኖ አሌግሪ በ ዛሬው መርሐ ግብር 400ኛ ጨዋታቸውን በ አሰልጣኝነት በ ሴርያው መርተዋል ።
• ጁቬንቱስ በ ተከታታይ ሀያ የ ሴርያው ጨዋታቸውን ግብ ተቆጥሮባቸዋል ።
• አዲሱ የ ጁቬንቱስ ተጫዋች ማኑኤል ሎካቴሊ በ ጨዋታው ግብ ከ ማስቆጠር ባለፈ ለ ግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• የ መሪነቱን ግብ ያስቆጠረው ፓውሎ ዲባላን ጨምሮ አልቫሮ ሞራታ ባጋጠማቸው ጉዳት ከ ሜዳ ተቀይረው ሊወጡ ተገደዋል ።
• ጁቬንቱስ በቀጣይ በ አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ከ ቼልሲ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ።