የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በሳምንቱ ተጠባቂ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድን 5 ለ 0 አሸንፈዋል ።
• ሳላህ በሊጉ ባደረጋቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች አስር ጎሎችን ሲያስቆጥር አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ሊቨርፑል በ ዩናይትድ ላይ አምስት ጎሎችን በ ኦልድ ትራፎርድ ሲቆጥርባቸው ከ ሰማንያ አምስት አመት በኋላ ነው ።
• ዩናይትዶች በሁሉም የውደድር መድረክ በሜዳቸው ባደረጓቸው ተከታታይ አስራ ሶስት ጨዋታዎች ግብ ተቆጥሮባቸዋል ።
• ማንችስተር ዩናይትዶች በተከታታይ ሶስት ጨዋታዎች ከ አንድ በላይ ግቦች ሊቆጠርባቸው ችሏል ።
• ሞሀመድ ሳላህ ለተከታታይ አስረኛ ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል ።
• ሳላህ በ ድሮግባ በሊጉ ተይዞ የነበረውን የ አፍሪካ ከፍተኛ ግብ አግቢነት በ 107 ጎሎች የግሉ አድርጓል ።