• ሮበርት ሊዋንዶውስኪ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊጉ ለ ባየር ሙኒክ 100ኛ ጨዋታውን አድርጓል ።
• በሴርያው ደካማ ጉዞ ላይ የሚገኙት ጁቬንቱሶች በ ሻምፒየንስ ሊጉ ከወዲሁ አስራ ስድስት ውስጥ መግባታቸውን አረጋግጠዋል ።
• ሊዋንዶውስኪ ሀያ ስምንተኛ ሀትሪኩን በእግር ኳስ ህይወቱ መስራት ችሏል ።
• ሮናልዶ በአራት ተከታታይ የ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠር የቻለ ቀዳሚው የ ዩናይትድ ተጫዋች ነው ።
• ሊዋንዶውስኪ በ ዘንድሮው የውድድር ዓመት በ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊጉ በ አራት ጨዋታዎች ስምንት ጎሎችን አስቆጥሯል ።
• የ አታላንታው የፊት መስመር አጥቂ ዱቫን ዛፓታ በ አስር የሻምፒየንስ ሊግ ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ሲያደርግ የ ክለቡ ቀዳሚው ተጫዋች አድርጎታል ።
• ሊሮይ ሳኔ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ስምንት ጎሎችን ሲያስቆጥር ስምንት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ሊዋንዶውስኪ ያስቆጠራቸው ስምንት ጎሎች በ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊጉ እየተሳተፉ ከሚገኙ ክለቦች መካከል ከ ሀያ ስድስቱ የበለጠ ነው ።