በአውሮፓ ዋንጫው እየወጡ ባሉ ደረጃዎች መካከል የክለቦች የአካዳሚ ተጫዋቾች በሀገራት ላይ ያላቸው ተፅዕኖ ዋነኛው ነው ።
በተሰራ ጥናት መሰረት ስዋንሲ ሲቲ በአካዳሚው ተጫዋቾች በአውሮፓ ዋንጫ ከ ሌሎች ክለቦች ጋር በጋራ አስረኛ ደረጃን ይዘዋል ።
ስዋንሲ ሲቲ በተለይም ከ ሻምፒየንስ ሺፑ ቀደሚው ክለብ ሲሆን በርካታ አድናቆት እየጎረፈላቸው ይገኛል ።
አያክስ አስራ ስድስት የአካዳሚውን ተጫዋቾን ማስመረጡ አለማስገረሙ እየተነገረ ይገኛል ፣ በኔዘርላንድስ ብሔራዊ ቡድን እንዲሁም በ ቤልጂየም ፣ በዴንማርክ እና በሃንጋሪ ላይ አሻራዎቹን ማሳረፍ ችሏል ፡፡
ማንችስተር ሲቲ በአስራ አንድ ተጫዋቾች ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ ባየር ሙኒክ ፣ ቼልሲ እና ቤንፊካ ብዛት ያላቸውን የአካዳሚ ተጫዋቾች ያሳተፉ ሌሎች ክለቦች ናቸው ።
ማንችስተር ዩናይትድ ስድስት የአካዳሚ ተጫዋቾቹን ማስመረጥ ሲችሉ የ ሜሰን ግሪን ውድ በጉዳት አለመካተት ምርጥ አስር ውስጥ እንዳይካተቱ አድርጓቸዋል ።