ከ ስኮት ፓርከር ጋር ከቀናት በፊት መለያየታቸው የተገለፀው ፉልሀሞች አዲስ አሰልጣኝ መሾማቸው ተገልጿል ።
ፉልሀም የ 41 ዓመቱን ማርኮ ሲልቫ ለ ቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የክለቡ ዋና አሰልጣኝ በማድረግ መሾማቸው ይፋ ሆኗል ።
የቀድሞ አሰልጣኝ ስኮት ፓርከር ከቀናት በፊት ዕለተ ሰኞ ከ ቡድኑ ጋር ሲለያይ ማረፊያው ቦርንማውዝ ማድረጉ የሚታወስ ነው ።
አዲሱ የፉልሀም አሰልጣኝ ለሊጉ አዲስ ያልሆነ ሲሆን ከዚህ ቀደም በ ሁል ሲቲ ፣ ኤቨርተን እና ዋትፎርድ በማሰልጠን ማሳለፉ ይታወሳል ።