የ መርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ወደ ኤላንድ ሮድ አቅንተው ሊድስ ዩናይትድን አሸንፈው መመለስ ችለዋል ።
• ሞሀመድ ሳላህ ፣ ማኔ እና ፋቢንሆ የ ሊቨርፑልን የ ማሸነፊያ ጎሎች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው ።
• ሳላህ በ ሊጉ ያስቆጠራቸውን የ ግብ መጠን ወደ 100 ከፍ ማድረግ ችሏል ።
• ሀርቪ ኢሊዮት ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል ።
• ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑሎች አራት ደረጃዎችን በ ማሻሻል በ አስር ነጥቦች ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።