በ አምስተኛ ሳምንት የ ሊጉ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትዶች በ ሮናልዶ እና ሊንጋርድ ግብ ድል ቀንቷቸዋል ።
• ቤንርሀማ ዌስትሀምን ቀዳሚ ያደረገች ግብ ቢያስቆጥርም ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ጄሲ ሊንጋርድ ለ ቀያይ ሴጣኖቹ የ ማሸነፊያ ጎሎች አስቆጥረዋል ።
• ሮናልዶ ወደ ዩናይትድ ከተመለሰ በኋላ ባደረጋቸው ሁሉም ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠር ችሏል ።
• ሮናልዶ በ ሶስት ጨዋታዎች ለ ቀያይ ሴጣኖቹ አራት ጎሎችን ከ መረብ አሳርፏል ።
• ዴቪድ ዴህያ በ ጭማሪ ደቂቃ ፍፁም ቅጣት ምት በ ማዳን ቡድኑን አቻ ከ መውጣት ታድጓል ።